"Ethical Generations, Systematic Institutions!"
"ትዉልድን በሥነ ምግባር፤ ተቋምን በአሰራር!"
የአማራ ክልል የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን
የአማራ ክልል የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ኮሚሽኑን እንደገና መልሶ ለማቋቋም በወጣው አዋጅ ቁጥር 237/2008 መሠረት የተቋቋመ መንግስታዊ ተቋም እና በስሩ ደሴ ጎንደር ደ/ብርሀን ቅርንጫፍ ጽ/ቤቶችን እንዲሁም የዞን ፣የወረዳ እና የተቌማትን የሥነ ምግባር መከታተያ ክፍሎችን በማደራጀት እና በመምራት የሥነ ምግባር ግንባታ እና የፀረ-ሙስና ትግሉን አሳታፊ በሆነ መንገድ የሚመራ መንግስታዊ ተቋም ነው፡፡
ኮሚሽኑ ሙስናና ብልሹ አሰራርን ለመከላከል ከሚያከናውናቸው ተግባራት መካከል አስቸኳይ የሙስና መከላከል፣የተቐም የአሰራር ስርዓት ጥናት ሀብት ምዝገባ እና የማሳወቅ ስራን ማከናወን አንዱ ተግባር ነው፡፡
ተቐማት አሰራራቸው ከሙስናና ብልሹ አሰራር የፀዳ ይሆን ዘንድ በትኩረት የምንሰራ ሲሆን በተጨማሪም ሀብትን ማሳወቅና ማስመዝገብ የመንግስትን አሰራር በግልፅነትና በተጠያቂነት ለመመስረት ከፍተኛ ጠቀሜታ ያለው በመሆኑ ተመራጮች፣ ተሿሚዎችና የሚመለከታቸው የመንግሥት ሠራተኞችን ሀብትና ጥቅማቸውን እንዲያሳውቁ፣ እንዲያስመዘግቡና እንዲያሳድሱ እየተደረገ ይገኛል፡፡ በመሆኑም የዘጠኝ ወር የዕቅድ ክንውን አፈፃፀም ሪፖርት እንደሚከተለው ቀርቧል፡፡
ክልል ዓቀፍ የፀረ- ሙስና ጥምረት ከሀላፊዎች እና ፣ከሲቪክ ማህበረሰብ የተውጣጣ ጥምረት ተችሏል፡፡
የአማራ ክልል የስነ-ምግባርና የፀረ-ሙስና ኮሚሽን ዋናዋና ተግባራት
-
ሙስናን አልቀበልም፤ ሙስናን አልሰጥም!
ህግን እናከብራለን፣ በሀቀኝነት እንኖራለን።
የህዝብን ንብረት እንጠብቃለን!
-
ቁልፍ መርሆዎ
ታማኝነት (Trust) - በሰዎች መካከል ጠንካራ ግንኙነት ለመፍጠር።
ፍትህ (Fairness) - ሁሉም እኩል መብት እንዲኖረው ለማድረግ።
የጋራ እሴቶች (Shared Values) - ማህበረሰቡ በአንድነት በሰላም እንዲኖር።
-
የተማሪዎች ውድድር
-
የሀብት ምዝገባ ሲያካሂዱ
